ለሥራ ብቁ ያልሆኑ ደካሞችን መርዳት
በጤናም ሆነ በእርጅና ምክንያት መሥራት የማይችሉ ሰዎችን በቀሪው የሕይወት ዘመናቸው በክብርና በደስታ መኖር እንዲችሉ እንክብካቤ እናደርጋለን፤ ይህንን አርአያነት ያለው ተግባርም በሰፊው ለማዳረስ እየሠራን እንገኛለን፡፡
ሴቶችን በማብቃት፣ የህፃናትን መብት በማስከበር እና ለአረጋውያን እንክብካቤ በማድረግ የተሻለ ማህበረሰብ መገንባት።
መሰረታችን
"ደካማ ወገንን መርዳት የዕድገት መሰላል እንጅ ውድቀትን አያመጣም"
እነዚህ ሦስት ምሶሶዎች የዕለት ተዕለት ሥራችንን ይመራሉ፡፡
በጤናም ሆነ በእርጅና ምክንያት መሥራት የማይችሉ ሰዎችን በቀሪው የሕይወት ዘመናቸው በክብርና በደስታ መኖር እንዲችሉ እንክብካቤ እናደርጋለን፤ ይህንን አርአያነት ያለው ተግባርም በሰፊው ለማዳረስ እየሠራን እንገኛለን፡፡
ሥራ በችሎታ ላይ የተመሠረተ መሆን አለበት እንጂ ጾታን መሰረት ያደረገ መሆን የለበትም፡፡ ሴቶች በቤታቸውም ሆነ ከቤት ውጭ ውሳኔዎችን እንዲያሳልፉ፣ የሙያ ሥልጠናዎችን እንዲያገኙ፣ እንዲሁም ራሳቸውንና ቤተሰባቸውን መደገፍ እንዲችሉ አቅማቸውን እናበቃለን፡፡
በጥሩ ሥነ-ምግባር የታነጸ እና ብቁ ትውልድ ማፍራትን ዓላማ በማድረግ፣ ሕፃናት ገና ከልጅነታቸው ጀምሮ መደበኛ ትምህርት እና የሥነ-ምግባር እውቀትን የማግኘት መብታቸውን እንጠብቃለን፡፡
ስለ እኛ
የአውራ አምባ ማኅበረሰብ በክቡር ዶ/ር ዙምራ ኑሩ ሐሳብ አመንጪነት፣ በ1964 ዓ.ም በአርሶ አደር አባላት ጥምረት በአምስት መሠረታዊ መርሆዎች ላይ የተመሰረተ ነው፡፡
የሴቶችን እኩልነት በማክበር፣ የሕፃናትን መብት በማስጠበቅ፣ በጤናም ሆነ በእርጅና መሥራት የማይችሉትን በመርዳት፣ መጥፎ አነጋገር እና አሰራርን በማስወገድ እና ጥቅል ወገንተኝነትን በማጠናከር የተሻለ ማኅበረሰብ ለመገንባት እንተጋለን፡፡
ዋና ሥራችን
የአውራ አምባ ማኅበረሰብ አዲስ ምዕራፍ ባህሪና ልማት ግንባታ ሁለገብ ማኅበር ለሰብአዊነት ካበረከተው የአምስት አሥርት ዓመታትን የተሻገረ የአገልግሎት ልምድ ላይ የተመሠረተ፡፡
በጤናም ሆነ በእርጅና ምክንያት ለሥራ ብቁ ያልሆኑ ደካሞችን መንከባከብ እና ቀሪ ህይወታቸውን በደስታ እንዲመሩ ማስቻል።
ስለ ስርዐተ ጾታ እኩልነት በማስተማር እና የሙያ ስልጠናዎችን በመስጠት፣ ሴቶች ከጥገኝነትንና ድህነት እንዲወጡ አቅማቸውን ማሳደግ።
የህፃናት መብት መከበሩን ማረጋገጥ፣ እንዲሁም ከለጋ እድሜያቸው ጀምሮ የአካዳሚክ ትምህርቶችን እና የስነ-ምግባር እሴቶችን ማስተማር።
በድንገተኛ ችግሮች እንዲሁም በተፈጥሮ ወይም በሰው ሰራሽ አደጋዎች ምክንያት ለተጎዱ ሰዎች ልዩ ልዩ ድጋፎችን ማቅረብ።
በውይይት ላይ የተመሰረተ የግጭት አፈታት ባህልን ማዳበር፣ እንዲሁም የአገር በቀል ግጭት አፈታት ተሞክሮዎችን ለሌሎች ማህበረሰቦች ማስተማር።
የተፈጥሮ ሚዛን እንዳይዛባና ለቀጣዩ ትውልድ እንዲሻገር በተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ላይ መሥራት።
አገልግሎታችን
ስራችን ከ1964 ዓ.ም. ጀምሮ ባሉ የማይናወጡ መርሆች ላይ የተመሠረተ ነው፡፡ እነሱም፦ ለደካማ ወገኖች እንክብካቤ ማድረግ፣ የሴቶች እኩልነትን ማስፈን፣ ህፃናትን የትምህርት ዕድል እንዲያገኙ በማድረግ፣ የድንገተኛ አደጋ እርዳታ፣ ሰላም እና አካባቢ ጥበቃ ናቸው።
በጤና እክል ወይም በእድሜ መግፋት ምክንያት ለስራ ብቁ ላልሆኑ ሰዎች እንክብካቤ በማድረግ፣ ቀሪ ዘመናቸውን በደስታ እንዲኖሩ ማድረግ።
ሴቶች ሥራ እንዲሰሩ፣ ቤተሰቦቻቸውን እንዲደግፉ እንዲሁም ጥገኝነትን እና ድህነትን ትተው እንዲወጡ ለማስቻል በእኩልነት ላይ የተመሠረተ ትምህርት እና የሙያ ስልጠና በመስጠት አቅማቸውን ማጎልበት።
የቀጣዩ ትውልድ ብቁ እና በመርህ የሚመራ ሆኖ እንዲያድግ፣ የልጆችን የትምህርት፣ የአካዳሚክ እና የሞራል መብቶች በጋራ ማረጋገጥ።
ድንገተኛ ችግር ለገጠማቸው ሰዎች ተግባራዊ ድጋፍ መስጠት።
በውይይት አማካኝነት ግጭቶችን የመፍታት ባህልን ማስፋፋትና የማህበረሰባችንን የአገር በቀል የሰላም አሰራሮች ማካፈል
ከእኛ በኋላ ለሚመጡት ትውልዶች የተፈጥሮ ሚዛን እንዲጠበቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን መጠበቅ።
50+ ዓመታት - ከ1964 ጀምሮ
ከ1964 ጀምሮ በመተዛዘን፣ በእኩልነት እና በትብብር ህይወትን መለወጥ።
መረጃዎች በቁጥር
ስኬት ላይ እንዲደርሱ እና ራሳቸውን እንዲችሉ ድጋፍ ተደርጓል።
ለአረጋውያን ደስተኛ ሕይወት የሚሆን የእንክብካቤ ማዕከል ተቋቁሞ ተደራጅቷል።
ለተፈናቀሉ ወገኖች የዓይነት (የቁሳቁስ) ድጋፍ ተደራሽ ተደርጓል።
በሴቶች እኩልነት፣ በሕፃናት መብት እና በግጭት አፈታት ዙሪያ
እያንዳንዱ ተግባራችን ማኅበረሰቡን ማገልገል እና ለሁሉም ሰው የሚሆን የተሻለ ማኅበረሰብ መፍጠር ላይ ያተኮረ ነው።
ምንም እንኳን ስራዎችን ለረጅም አመታት በሰፊው ሲሰራ ቢቆይም እውቅናን አግኝቶ መስራት የጀመረው ግን ለ16 አመታት በክልል ደረጃ እንዲሁም 1 አመት በፌደራል ደረጃ አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል፡፡
በደግነት፣ በትጋት (በጠንካራ ስራ)፣ በእርስ በርስ መደጋገፍ እንዲሁም በመልካም ስነ ምግባር የታነፀ ትውልድን ለማፍራት።
ትውልዱ የሥራ ባህልን፣ ሥነ-ምግባርን፣ ፍቅርንና እርስ በርስ መከባበርን እንዲያዳብር የተለያዩ ስልጠናዎችንና ድጋፎችን በመስጠት፤ መልካም (ቅን) ትውልድ መገንባት እንዲቻል ለማድረግ።
መሠረታችን
የምናከናውነው ማንኛውም ተግባራት፣ በ1964 ዓ.ም. የአውራ አምባ ማህበረሰብ ሲመሰረት መጀመሪያ ላይ የተነሱትን እነዚህን መሰረታዊ ሀሳቦች መነሻ ያደረገ ነው።
በቤትም ሆነ በአስተዳደር የሴቶችን እኩልነት ማክበር።
በትምህርት፣ በደህንነት እና በክብር ረገድ የህፃናትን መብቶች ማክበር።
በጤናም ሆነ በእድሜ መግፋት ምክንያት መስራት የማይችሉ ሰዎችን መርዳትና መንከባከብ፤ እንዲሁም ወላጅ አልባ ህፃናትን ማሳደግ፣ ማስተማር እና ለስኬት ማብቃት።
መጥፎ አነጋገርና አሰራሮችን አስወግዶ በምትኩ መልካም አነጋገር አሰራሮችን ማጎልበት
የተበጣጠሰ ወገንተኝነትን በማስወገድ ሁሉም ወንድም ሁሉም እህት የሆነበት ጥቅል ወገንተኝትን ማጠንከር
ሥራችንን ይደግፉ