ደካማ ወገንን መርዳት የዕድገት መሰላል እንጅ ውድቀትን አያመጣም

ሴቶችን በማብቃት፣ የህፃናትን መብት በማስከበር እና ለአረጋውያን እንክብካቤ በማድረግ የተሻለ ማህበረሰብ መገንባት።

መሰረታችን

መሰረታችን

"ደካማ ወገንን መርዳት የዕድገት መሰላል እንጅ ውድቀትን አያመጣም"

ለሥራ ብቁ ያልሆኑ ደካሞችን መርዳት

በጤናም ሆነ በእርጅና ምክንያት መሥራት የማይችሉ ሰዎችን በቀሪው የሕይወት ዘመናቸው በክብርና በደስታ መኖር እንዲችሉ እንክብካቤ እናደርጋለን፤ ይህንን አርአያነት ያለው ተግባርም በሰፊው ለማዳረስ እየሠራን እንገኛለን፡፡

ሴቶችን ማበረታታት እና እኩልነትን ማረጋገጥ

ሥራ በችሎታ ላይ የተመሠረተ መሆን አለበት እንጂ ጾታን መሰረት ያደረገ መሆን የለበትም፡፡ ሴቶች በቤታቸውም ሆነ ከቤት ውጭ ውሳኔዎችን እንዲያሳልፉ፣ የሙያ ሥልጠናዎችን እንዲያገኙ፣ እንዲሁም ራሳቸውንና ቤተሰባቸውን መደገፍ እንዲችሉ አቅማቸውን እናበቃለን፡፡

ሕፃናት መብቶቻቸው ተከብሮ ያድጋሉ

በጥሩ ሥነ-ምግባር የታነጸ እና ብቁ ትውልድ ማፍራትን ዓላማ በማድረግ፣ ሕፃናት ገና ከልጅነታቸው ጀምሮ መደበኛ ትምህርት እና የሥነ-ምግባር እውቀትን የማግኘት መብታቸውን እንጠብቃለን፡፡

Awra Amba community members working together

ስለ እኛ

የአውራ አምባ ማኅበረሰብ

የአውራ አምባ ማኅበረሰብ በክቡር ዶ/ር ዙምራ ኑሩ ሐሳብ አመንጪነት፣ በ1964 ዓ.ም በአርሶ አደር አባላት ጥምረት በአምስት መሠረታዊ መርሆዎች ላይ የተመሰረተ ነው፡፡

የሴቶችን እኩልነት በማክበር፣ የሕፃናትን መብት በማስጠበቅ፣ በጤናም ሆነ በእርጅና መሥራት የማይችሉትን በመርዳት፣ መጥፎ አነጋገር እና አሰራርን በማስወገድ እና ጥቅል ወገንተኝነትን በማጠናከር የተሻለ ማኅበረሰብ ለመገንባት እንተጋለን፡፡

  • የሴቶች እኩልነት
  • የሕፃናት መብቶች
  • የአረጋውያን እንክብካቤ

ዋና ሥራችን

ዋና ዋና ፕሮግራሞቻችን

የአውራ አምባ ማኅበረሰብ አዲስ ምዕራፍ ባህሪና ልማት ግንባታ ሁለገብ ማኅበር ለሰብአዊነት ካበረከተው የአምስት አሥርት ዓመታትን የተሻገረ የአገልግሎት ልምድ ላይ የተመሠረተ፡፡

የአረጋውያን እንክብካቤ

የአረጋውያን እንክብካቤ

በጤናም ሆነ በእርጅና ምክንያት ለሥራ ብቁ ያልሆኑ ደካሞችን መንከባከብ እና ቀሪ ህይወታቸውን በደስታ እንዲመሩ ማስቻል።

ውጤት ፦ ላለፉት 30 ዓመታት ከ50 በላይ ለሚሆኑ አረጋውያን እንክብካቤ ተደርጓል።
ተጨማሪ ይመልከቱ
የሴቶችን አቅም ማሳደግ

የሴቶችን አቅም ማሳደግ

ስለ ስርዐተ ጾታ እኩልነት በማስተማር እና የሙያ ስልጠናዎችን በመስጠት፣ ሴቶች ከጥገኝነትንና ድህነት እንዲወጡ አቅማቸውን ማሳደግ።

ውጤት ፦ ከ250,000 በላይ ሴቶች ስለ እኩልነት ስልጠና አግኝተዋል።
ተጨማሪ ይመልከቱ
የህፃናት የመማር መብት

የህፃናት የመማር መብት

የህፃናት መብት መከበሩን ማረጋገጥ፣ እንዲሁም ከለጋ እድሜያቸው ጀምሮ የአካዳሚክ ትምህርቶችን እና የስነ-ምግባር እሴቶችን ማስተማር።

ውጤት ፦ ከ300 በላይ ህፃናት ራሳቸውን እንዲችሉ ተደርገው ተምረዋል።
ተጨማሪ ይመልከቱ
የአደጋ ጊዜ ድጋፍ

የአደጋ ጊዜ ድጋፍ

በድንገተኛ ችግሮች እንዲሁም በተፈጥሮ ወይም በሰው ሰራሽ አደጋዎች ምክንያት ለተጎዱ ሰዎች ልዩ ልዩ ድጋፎችን ማቅረብ።

ውጤት ፦ ከ600,000 ብር በላይ የሚገመት የእርዳታ አቅርቦት ተደራሽ ተደርጓል።
ተጨማሪ ይመልከቱ
የግጭት አፈታት

የግጭት አፈታት

በውይይት ላይ የተመሰረተ የግጭት አፈታት ባህልን ማዳበር፣ እንዲሁም የአገር በቀል ግጭት አፈታት ተሞክሮዎችን ለሌሎች ማህበረሰቦች ማስተማር።

ውጤት፦ ከ50 ዓመታት በላይ የዘለቀ የሰላም ህይወት ተሞክሮ
ተጨማሪ ይመልከቱ
የአካባቢ ጥበቃ ስራ

የአካባቢ ጥበቃ ስራ

የተፈጥሮ ሚዛን እንዳይዛባና ለቀጣዩ ትውልድ እንዲሻገር በተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ላይ መሥራት።

ውጤት፦ ስኬታማ የአፈር ጥበቃ እና የዛፍ ተከላ ስራዎች ተከናውነዋል።
ተጨማሪ ይመልከቱ

አገልግሎታችን

ከአምስት አስርት ዓመታት በላይ የተሻገረ የማህበረሰብ ተሞክሮ

ስራችን ከ1964 ዓ.ም. ጀምሮ ባሉ የማይናወጡ መርሆች ላይ የተመሠረተ ነው፡፡ እነሱም፦ ለደካማ ወገኖች እንክብካቤ ማድረግ፣ የሴቶች እኩልነትን ማስፈን፣ ህፃናትን የትምህርት ዕድል እንዲያገኙ በማድረግ፣ የድንገተኛ አደጋ እርዳታ፣ ሰላም እና አካባቢ ጥበቃ ናቸው።

በጤና እክል ወይም በእድሜ መግፋት ምክንያት ለስራ ብቁ ላልሆኑ ሰዎች እንክብካቤ በማድረግ፣ ቀሪ ዘመናቸውን በደስታ እንዲኖሩ ማድረግ።

ሴቶች ሥራ እንዲሰሩ፣ ቤተሰቦቻቸውን እንዲደግፉ እንዲሁም ጥገኝነትን እና ድህነትን ትተው እንዲወጡ ለማስቻል በእኩልነት ላይ የተመሠረተ ትምህርት እና የሙያ ስልጠና በመስጠት አቅማቸውን ማጎልበት።

የቀጣዩ ትውልድ ብቁ እና በመርህ የሚመራ ሆኖ እንዲያድግ፣ የልጆችን የትምህርት፣ የአካዳሚክ እና የሞራል መብቶች በጋራ ማረጋገጥ።

ድንገተኛ ችግር ለገጠማቸው ሰዎች ተግባራዊ ድጋፍ መስጠት።

በውይይት አማካኝነት ግጭቶችን የመፍታት ባህልን ማስፋፋትና የማህበረሰባችንን የአገር በቀል የሰላም አሰራሮች ማካፈል

ከእኛ በኋላ ለሚመጡት ትውልዶች የተፈጥሮ ሚዛን እንዲጠበቅ የተፈጥሮ ሀብቶችን መጠበቅ።

ውጤታችን

የለውጥ ታሪኮች

ከዚህ በፊት በተሰሩ ስራዎች የተመዘገቡ ውጤቶችን ይመልከቱ ።

50+ ዓመታት - ከ1964 ጀምሮ

በሰው ልጆች ክብር እና በእኩልነት ላይ የተገነባ የማህበረሰብ ተፅዕኖ

ከ1964 ጀምሮ በመተዛዘን፣ በእኩልነት እና በትብብር ህይወትን መለወጥ።

መረጃዎች በቁጥር

ስኬቶች

300+ የተማሩ ልጆች

ስኬት ላይ እንዲደርሱ እና ራሳቸውን እንዲችሉ ድጋፍ ተደርጓል።

50+ እንክብካቤ የተደረገላቸው አረጋውያን

ለአረጋውያን ደስተኛ ሕይወት የሚሆን የእንክብካቤ ማዕከል ተቋቁሞ ተደራጅቷል።

600,000+ የቀረበ የዓይነት (የቁሳቁስ) እርዳታ

ለተፈናቀሉ ወገኖች የዓይነት (የቁሳቁስ) ድጋፍ ተደራሽ ተደርጓል።

250,000+ ሥልጠና የወሰዱ ሰዎች

በሴቶች እኩልነት፣ በሕፃናት መብት እና በግጭት አፈታት ዙሪያ

100% ማኅበረሰቡን ማዕከል ያደረገ

እያንዳንዱ ተግባራችን ማኅበረሰቡን ማገልገል እና ለሁሉም ሰው የሚሆን የተሻለ ማኅበረሰብ መፍጠር ላይ ያተኮረ ነው።

ምንም እንኳን ስራዎችን ለረጅም አመታት በሰፊው ሲሰራ ቢቆይም እውቅናን አግኝቶ መስራት የጀመረው ግን ለ16 አመታት በክልል ደረጃ እንዲሁም 1 አመት በፌደራል ደረጃ አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል፡፡

ራዕይ

በደግነት፣ በትጋት (በጠንካራ ስራ)፣ በእርስ በርስ መደጋገፍ እንዲሁም በመልካም ስነ ምግባር የታነፀ ትውልድን ለማፍራት።

ተልዕኮ

ትውልዱ የሥራ ባህልን፣ ሥነ-ምግባርን፣ ፍቅርንና እርስ በርስ መከባበርን እንዲያዳብር የተለያዩ ስልጠናዎችንና ድጋፎችን በመስጠት፤ መልካም (ቅን) ትውልድ መገንባት እንዲቻል ለማድረግ።

መሠረታችን

አምስቱ ዋና ዋና መርሆቻችን

የምናከናውነው ማንኛውም ተግባራት፣ በ1964 ዓ.ም. የአውራ አምባ ማህበረሰብ ሲመሰረት መጀመሪያ ላይ የተነሱትን እነዚህን መሰረታዊ ሀሳቦች መነሻ ያደረገ ነው።

  1. የሴቶች እኩልነት

    በቤትም ሆነ በአስተዳደር የሴቶችን እኩልነት ማክበር።

  2. የህፃናት መብቶች

    በትምህርት፣ በደህንነት እና በክብር ረገድ የህፃናትን መብቶች ማክበር።

  3. አቅመ-ደካሞችን መደገፍ

    በጤናም ሆነ በእድሜ መግፋት ምክንያት መስራት የማይችሉ ሰዎችን መርዳትና መንከባከብ፤ እንዲሁም ወላጅ አልባ ህፃናትን ማሳደግ፣ ማስተማር እና ለስኬት ማብቃት።

  4. መጥፎ አሰራርንና አነጋገርን ማስወገድ

    መጥፎ አነጋገርና አሰራሮችን አስወግዶ በምትኩ መልካም አነጋገር አሰራሮችን ማጎልበት

  5. ጥቅል ወገንተኝት

    የተበጣጠሰ ወገንተኝነትን በማስወገድ ሁሉም ወንድም ሁሉም እህት የሆነበት ጥቅል ወገንተኝትን ማጠንከር

ሙሉውን ታሪክ ያንብቡ ያሳካናቸውን ስኬቶች ይመልከቱ

ሥራችንን ይደግፉ

ያግኙን